Friday, May 3, 2013

ሰበር ዜና ተብሎ የተሰበረ ፍርድ ውሰኔ ተላለፈ

ሰበር ዜና ተብሎ የተሰበረ ፍርድ ውሰኔ ተላለፈ
     በግሩም ተ/ሀይማኖት
    የዛሬውን ሰበር ዜና ያስነበበን ወሰንሰገድ ነው፡፡ እሱ ያለውን የተከወነውን ነው የሳየን፡፡ ተባረክ ስለው የፈረደውን ዳኛ ምን ማለት እንዳለብኝ አላሰብኩምና አልረግመውም አልመርቀውም፡፡ የታዘዘውን ፈጻሚ ነውና ምን ማለትስ ይቻላል፡፡ ፍትህ ባልነገሰበት ፍትህ መጠበቅ ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ እንደሚባለው ነው፡፡ ቴሌቪዥኔን እንደፈለኩ በሪሞት ኮንትሮሉ እንደምዝረው ሁሉ እነሱም እንደፈለጉ የሚያዙት የፍትህ አካላት አዋቅረው ህገ-መንግስት ብለው ያጸደቁትን ሲሽሩት ማየትስ ይሄ የመጀመሪያ ነው እንዴ? ወያኔን የተቃወመ ሁሉ አሸባሪ የሚባልበት ፎርሙላስ የተፈበረከው በእነሱ አይደለ?
     ጠቅላይ ፍርድ ቤቱን በደንብ የተመላለስኩበት የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር የአሁኑ ፓስተር ታምራት ላይኔ በሙስና ተከሰው ይመላለሱበት በነበረ ጊዜ ነው፡፡ በዛን ወቅት የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር ታምራት ላይኔ ‹‹ክቡር ዳኛ ዝም ብለው የታዘዙትን ይፍረዱ..በስልክ ምን እንደሚሰራ እናውቃለን እኮ….›› ብለው ረዘም ያለ ነገር የተናገሩት ሁሌም ትዝ ይለኛል፡፡ በሚያዘውቁበት፣ ባዘዙበት አፋቸው የነገሩን እውነታ ዛሬም አለመለወጡ ይታወቃል፡፡ ስለዚህ ‹‹..በእነ አንዱዓለም አራጌ እና በጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ላይ የተላለፈው ፍርድ /// ቤት ፀና፡፡…›› መጀመሪያ አሸባሪ ብለው ያለ ምንም ማስረጃ ሲፈርዱ ያላፈሩ የተፈረደውን ማጽደቅ ምን ገዷቸው ይፈሩ? ለመሆኑ ‹‹..እነ አንዱዓለም አራጌ ያቀረቡትን ይግባኝ መርምሮ የመጨረሻ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው // ቤት ዛሬ ሚያዝያ 24 ቀን 2ዐዐ5 ዓ.ም በሰጠው ብይን፣ ይግባኝ ባዮች በሽብርተኛነት ተግባር ላለመሳተፋቸው አሳማኝ የሆነ መከላከያ አላቀረቡም ብሏል፡፡ በዚህ የተነሳ የከፍተኛውን /ቤት ውሳኔ ሙሉ በሙሉ አፅንቷል፡፡…›› እዚህች ጋር አንድ ነገር ለማየት እንሞክር፡፡
     መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤቱ አሸባሪ ብሎ ሲወስንባቸውስ አቃቢ ህግ ያቀረባቸው ማስረጃዎች ብቁ ነበሩ ወይ? ያኔ ምን አይተው ፈረዱ አሁንስ እሱ ብቁ ሆኖ ነው ያጸደቁት? የሚለውን ማየት በቂ ነው፡፡ እውነት ተደብቆ አይቀርምሲል እስክንድር ነጋ ከፍርዱ በኋላ በችሎት ውስጥ መነገሩም ተዝግቧል፡፡ አንድ ቀን እውነት እንደሚወጣ እነሱስ ሳያውቁ ቀርተው ነው? ህሊናቸውን ሸጠው ሆነ እንጂ፡፡ ያኔም እነ እስክንድር አንገታቸውን ሲያቃኑ እነሱ ያፍራሉ ብዬ አልጠብቅም፡፡ ትላንት የልባቸውን የሰሩ ህዝብ ያስጨፈጨፉ ሁሉ ተገደን ነው ምን እናድርግ ሲሉት ህዝቡ ስለሚያምናቸው እነዚህም ‹‹ተገደን ነው›› ይሉናል፡፡ ይልቅየተከራከርነው ፍትህ እናገኛለን ብለን አይደለም፤ ፍትህ ወዳድ በመሆናችን ነውየምትለው የናትናኤል አነጋገር ትመቻለች፡፡