Thursday, April 25, 2013

አፍሪካ ስደተኞች

አፍሪካ
የመላ አፍሪካ የወንጀል ጉባዔ ባሕርዳር ላይ እየተካሄደ ነው

አፍሪካ ውስጥ ሰዎችን በሕገወጥ መንገድ እና ለሕገወጥም ጉዳዮች ማሸጋገር፣ መድኃኒቶችን፣ ማዕድናትን፣ እንደዝሆን ጥርስ የመሣሰሉ የተከለከሉ አደኖች ውጤቶችንና ሌሎችም ሃብቶችና ሸቀጣሸቀጥ በሕገወጥ መንገድ ማንቀሣቀስና ማስተላለፍ ሁል ጊዜ ችግር ሆኖ መቆየቱ ይታወቃል፡፡

መንግሥታቸውን እየሸሹ በሚጠፉ ኤርትራዊያን ላይ እየተፈፀመ ነው የሚባለው አዲስ ዓይነት ንግድ ግን ቀድሞ ያልታየ አስፈሪና ዘግናኝ አድራጎት ታሪኮችን ፈጥሯል፡፡
የሲናይ ቁስልየሲናይ ቁስል

ኤርትራዊያኑ ስደተኞች ሱዳን ውስጥ ተጠልፈው ወደ ግብፅ ይሸጡና ቤተሰቦቻቸው ቤዛ የሚሆን ገንዘብ እስኪልኩ በስቃይ ውስጥ እንዲቆዩ ይደረጋሉ፡፡

ይህንንና መሰል ኢሰብአዊና ድንበር አቋራጭና የተደራጁ የወንጀል አድራጎቶችን አንስቶ የሚመክር የመላ አፍሪካ ጉባዔ ኢትዮጵያ ውስጥ ባሕርዳር ከተማ ላይ እየተካሄደ ነው፡፡

ሜሮን እስጢፋኖስ በባሕርዳሩ ጉባዔ ላይ ለመሣተፍ ኢትዮጵያ ውስጥ ይገኛሉ፡፡ የኤርትራ ተወላጅዋ ስዊድናዊት የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ሜሮን በቀን ከ15 እስከ ሃያ የሚደርሱ ኤርትራዊያን ስደተኞችን የስልክ ጥሪዎች ይቀበላሉ፡፡ ስብሰባው እየተካሄደ ሣለ ከቪኦኤ ጋር ለመነጋገር ወጣ ያሉ ጊዜ የእጅ ስልካቸውን ሲመለከቱት የተደረደሩት ያመለጧቸው ወይም ያልመለሷቸው ስልኮች ብዛት ያስደነግጥ ነበር አለች፤ የዚህ ዘገባ አጠናቃሪ ሃና ማክኔሽ፡፡

ሜሮን የሚያነጋግሯቸው ብዙዎቹ ኤርትራዊያን የሚደውሉት በሚደርስባቸው በጠላፊዎቻቸው ወይም በገዥዎቻቸው በሚደርስባቸው ሥቃይ መከራቸውን እያዩ ነው፡፡

“እያሰቃዩሽ ቤተሰቦችሽ ወይም ወላጆችሽ ጋ ይደውላሉ፡፡ እኔ ከአንዲት ልጅ እናት ጋር ተነጋግሬ ነበር፡፡ ልጅዋ በአምስት ወንዶች ስትደፈር እንድትሰማ ያደርጉ ነበር፡፡ የማስለቀቂያው ክፍያ ከሰላሣ ሺህ እስከ ሃምሣ ሺህ ዶላር ይደርሣል፡፡ አማራጭ ስታጣ፣ ካለህ ትከፍላለህ፤ ካለበለዚያም ትሞታለህ፡፡ እንዲህ ዓይነቱ አድራጎት እየተፈፀመ ያለው እአአ ከ2009 ዓ.ም ጀምሮ ነው፡፡ ዓለምአቀፉ ማኅበረሰብ ግን እያየ እንዳለየ መሆንን መርጧል፡፡” ብለዋል ሜሮን እስጢፋኖስ፡፡
ሲናይሲናይ

እሥራኤል የአፍሪካዊያን ስደተኞችን የሥራ ፍቃድ በመንጠቋና ዓለምአቀፍ ለጋሾች ደግሞ ወደአውሮፓ የሚነጉደውን የስደተኛ ማዕበል ገታ እንዲያደርጉላቸው ለቀድሞው የሊብያ መሪ ሙአማር አል ከዛፊ ሰጥተው ስለነበረ ቀደሞ ሕገወጥ አስተላላፊ የበሩት አሁን የተያያዙትን አዲሱን ዓይነት የሥቃይ ንግድ ጀመሩና ገበያውንም አደሩት፡፡
ከሲናይ የእሥርና ማሰቃያ ሠፈሮች አንዱከሲናይ የእሥርና ማሰቃያ ሠፈሮች አንዱ

ድንበር እያቋረጠ የሚያመልጥ ዜጋ ቢገኝ ተኩሶ የሚገድለውን የኤርትራን መንግሥት እየሸሹ ከሃገር የሚጠፉ ኤርትራዊያን ቁጥር በወር ወደ ሦስት ሺህ እንደሚደርስ አንድንድ የረድዔት ድርጅቶች ይናገራሉ፡፡
ከሲናይ የእሥርና ማሰቃያ ሠፈሮች አንዱከሲናይ የእሥርና ማሰቃያ ሠፈሮች አንዱ

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳዮች ከፍተኛ ኮሚሽነር - ዩኤንኤችሲአር እንደሚለው በመላ አፍሪካ ቀንድ ውስጥ ከሩብ ሚሊየን በላይ ኤርትራዊያን ስደተኞችና ወደ 15 ሺህ የሚሆኑ ደግሞ የፖለቲካ ጥገኝነት ጠያቂዎች ይገኛሉ፡፡

የኤርትራ መንግሥት ዜጎቹ ከሃገር ለመውጣታቸው እንዲከፍሉ ያደረጋል እየባለ ይወቀሣል፡፡ ሸሽተው የወጡ ሰዎችን ቤተሰቦች እንደሚቀጣ፣ በውጭ ሃገሮች የሚገኙ ኤርትራዊያን ከገቢያቸው 2 ከመቶ ታክስ እንዲከፍሉ በገሃድ የማይታዩ ግን አስገዳጅ የሆኑ ዘዴዎችን እንደሚጠቀም ይነገራል፡፡
ሲናይሲናይ

ተደጋግሞ እንደሚሰማውና ዓለምአቀፎቹ ድርጅቶችም እንደሚሉት ብዙ ኤርትራዊያን ሱዳን ውስጥ ከሚገኙ የስደተኛ መጠለያ ሠፈሮች እየታፈኑና እየተጠለፉ ግብፅ ውስጥ ላሉ በደዊኖች ለሚባሉ የተለያዩ ጎሣዎች አባላት ይሸጣሉ፡፡

ከስዊድን የፖለቲካ ወገናዊነት የሌለው የኤርትራ ዜና የራዲዮ ሥርጭት ሥራ የሚያካሂዱት ሜሮን እስጢፋኖስ ሁሉም እጁን አጣጥፎ ባለበት ሁኔታ እጅግ ዘግናኝ የሆኑ የጭካኔ አድራጎቶች እንደሚካሄዱ ይናገራሉ፡፡ “በየቀኑ ለአራት ሰዓታት እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ ቸንክረው ይሰቅሏቸዋል፡፡ ወንዶቹንም ሴቶቹንም በቡድን ይደፍሯቸዋል፡፡ ታጋቾቹ እርስ በራሣቸውም እንዲደፋፈሩ ያስገድዷቸዋል፡፡” ብለዋል ለቪኦኤ በሰጡት ቃል፡፡

“በሺሆች የሚቆጠሩ በእንዲህ ዓይነት ጠለፋና ሥቃይ ውስጥ አልፈዋል” የሚሉት ሜሮን ወደ መቶ የሚሆኑ ሰዎች ደግሞ አሁንም በጠላፊዎቹ እጆች ውስጥ እንደሚገኙ አመልክተዋል፡፡
የሲናይ ጠባሣየሲናይ ጠባሣ

በአፍሪካ ቀንድ የአውሮፓ ኅብረት ተጠሪ አሌክሣንደር ሮንዶስ “ይህ ዓለም ሊነቃበት የሚገባ ችግር ነው” ይላሉ፡፡ “ለምን እንዲህ ዓይነት ይደረጋል ብሎ ከመጠየቅ ይልቅ እንዲህ ዓይነት አስፈሪና ቀፋፊ ነገር አሁን እየተፈፀመ መሆኑን መረዳት ይከብዳል፤ ይህ ዓይነተኛ የፍፁም ግድየለሽነት መገለጫ ነው፡፡” ብለዋል ሚስተር ሮንዶስ፡፡

የዚህ “ዝም የተባለበት አሣዛኝ ታሪክ” ሲሉ ሮንዶስ የጠሩት አድራጎት ወሬ “በዓለም ሁሉ መናኘት፣ ለዓለም ሁሉ መሰማት አለበት” ብለዋል፡፡
በሲናይ የበደዊኖች መንደርበሲናይ የበደዊኖች መንደር

“ሰዎች ይህንን ታሪክ ከነ ሙሉ ዘግናኝነቱ ወይም አስፈሪነቱ ነው ማወቅ ያለባቸው፡፡ ይህ እራሱን የቻለ የባርያ ንግድ ዓይነት ነው፡፡ ቁጥሩ ሊገለፅ የማይችል ገንዘብ የባሕር ላይ ውንብድናን ወይም ፓይረሲን ለማስወገድ እናፈስሣለን፡፡ ይህኛው ግን እጅግ የባሰ በሰው ሕይወት ላይ የሚመነዘር በርካታ መዘዝ ያለው የውንብድና ዓይነት ነው፡፡” ሲሉ አክለዋል የአውሮፓ ኅብረቱ ተጠሪ፡፡

ሰዎቹ በብዙ ሃገሮች ውስጥ እያለፉና እየተሸጋገሩ ሕገወጥ ማስተላለፍንና የሰው ንግድን ለማስወገድ አንዳች እርምጃ ያለመወሰዱ የሚያሣየው አንዳች የተቀነባበረ የሙስና ሴራ ሊኖር የመቻሉን ነገር ነው ይላሉ የአውሮፓ ኅብረቱ ሮንዶስ፡፡
የሲናይ እንባየሲናይ እንባ

በሌላ በኩል ደግሞ ይህ ንግድ የሚካሄደው በሃያ አምስት ቤተሰቦች ወይም ጎጦች መሆኑንና በፍጥነት ማጥፋት የሚቻል መሆኑን ሜሮን አመልክተዋል፡፡

ባለፈው ዓመት አንድ የተጠለፈ እንግሊዛዊን ለማስለቀቅ በሲናይ ላይ ወረራ አካሂደው እንግሊዛዊውን ያስለቀቁት የግብፅ የፀጥታ ኃይሎች በሰንሠለት የታሠሩ፣ የተደበደቡ፣ በረሃብ የደከሙ፣ የጭካኔና የሥቃይ አያያዝ እየተፈፀመባቸው እንደነበረ በግልፅ የሚታዩ ሌሎች ሰዎችን አግኝተው ሣያስለቅቋቸው መመለሳቸውንም ሜሮን ገልፀዋል፡፡
የሲናይ እንግልትየሲናይ እንግልት

ይህ የኤርትራዊያኑ መጠለፍ ጉዳይ ትልቅ ችግር መሆኑን የሱዳን ፕሬዚዳንት ኦማር ሃሰን አል በሽር በዚሁ የኢትዮጵያው የወንጀል ጉዳይ ጉባዔ ላይ ማመናቸው ተዘግቧል፡፡

በግብፅም የወደቀው የሙባረክ አስተዳደር ባለሥልጣናት የበኩላቸውን እገዛ እንደሚያደርጉ ቃል ገብተው እንደነበረ ተጠቁሟል፡፡

አራት ዓመታት ካለፉ በኋላ ግን ችግሩ ተወግዶ አልታየም፤ እንዲያውም በዓለም ገፅ ላይ እጅግ በበረታ ድኅነት ውስጥ የሚማቅቁ ሕዝቦች በሚኖሩበት ጥግ በሚኖሩ ሰዎች ላይ ይህ ከመከራ የመገላገያ ቤዛ ክፍያ በብዙ እጅ አሻቀበ እንጂ፡፡
የሲናይ አሻራየሲናይ አሻራ

ይህ ስቃይና የሰው ልጅ መከራ ፍፃሜው ቅርብ እንዲሆን ብዙዎች ተስፋቸውን እየገለፁ ነው፡፡

Wednesday, April 24, 2013

ጠ/ሚ ሀ/ማሪያም ደሳለኝ ከጉማሬ ጋር ያመሳሰላቸው ሁለት ነገር

ጠ/ሚ ሀ/ማሪያም ደሳለኝ ከጉማሬ ጋር ያመሳሰላቸው ሁለት ነገር
   ቀባጠሩ ‹‹…ግመሎቹም ይሄዳሉ ውሾች ይጮሀሉ…››
ግሩም ተ/ሀይማኖት
      ሰውዬው ሲታዩ ራሳቸው ተረት ይመስላሉ ግን የቀድሞው ጠ/ሚ ሲተርቱ እና ሲሳቅላቸው ወይ ሲሳቅባቸው አይተው መተረት ደጋግመዋል፡፡አልሳቅንላቸውም አልሳቅንባቸውም አልቻሉበትም፡፡ ተናገር ተብለው የተላኩንት ለመናገር ፓርላማ ብቅ ብለው ነበር ዛሬ፡፡ ታዘው ከተናገሩት ሁሉ ያስገረመኝ አለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ድርጅት ሁማንራይትን በተመለከተ የተናገሩት ነው፡፡
   ‹‹..ሁማንራይትን በተመለከተ የቀረበ ጥያቄ አለ፡፡ የእነሱ ጉዳይ ግመሎቹ ይሄዳሉ ውሾቹ ይጮሀሉ..ነው፡፡…›› አሉ፡፡ የሰዎች መብት አልተከበረም ብሎ የሚጠይቅ ውሻ ሆኖ ለሆዱ ህሊናውን ሸጦ እንደ እቃ በሪሞት የሚዘወር እንደሳቸው አይነት ሲንቦል ምን ሊባል ነው አልኩና አሰብኩ፡፡ ታዲያ ማሰብ ነው እንጂ በምንም መሰዬ ትንፍሽ አላልኩም፡፡ አፈር ስሆን እንደሳቸው አይነትማ ጉማሬ ይባላል እንዳይሉኝ፡፡ ምክንያቱም በሁለት ነገር ስለሚመሳሰሉ እውነት ነው ታስብሉኛላችሁ፡፡ በመልክ ከመመሳሰል አልፎ ሌላም የሚያመሳስላቸው ነገር አለ፡፡ ታዲያ በአፍ በልቶ በአፍ መጸዳዳት ነው የሚያመሳስላቸው አላልኩም ልብ በሉ፡፡ እንደዛም ካልኩ ምኑ ነው ስህተት? ፓርላማ ውስጥ እንደዚህ ጭቃ ጅራፋቸውን ሲያወርዱት በአፍ ከመጸዳዳት በምን ይተናነሳል፡፡ ከጉማሬውስ በምን ተለይተዋል ማለት እችል ነበር፡፡ ‹‹…እዚህ ህዝብ ሲበጠብጥ ቆይቶ…›› ብለው ከሳቸው የማይጠበቅ ቃላት ተፉ፡፡ ለነገሩ ረስቼው ነው ከሳቸው የማይጠበቅ ያልኩት መቼ የራሳቸውን አውርተው ያውቃሉ፡፡
  ከቀረበላቸው ኩንታል ጥያቄ ውስጥ የአማራው ከቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል መፈናቀል አስመልክተው የቤንሻንጉል ባለስልጣናት ላይ ለጎዱላቸው፡፡ አጥረገረጉዋቸው፡፡ ያኙኛው እንዲህ በጎለደፈ አንደበት አልነበረም የሚለጉዱት፡፡ቢያንስ በዙሪያቸው ያሉ እንዲያጨበጭቡ አለያም እንዲያገጡ ያደርጉ ነበር፡፡ ትሻልን ሰድጄ ትብስን አመጣሁ ማለት ይሄኔ ነው፡፡ ለመሳደብ እንኳን የሚጠቀሙበት ቃላት በጣም የወረደ ነው፡፡ እነዚህን ባለስልጣናት ከነድንቁርናቸው፣ ከነሌብነታቸው አንስቶ ስልጣን ላይ ቂብ ያደረጋቸው እሳቸውን ከአፈር አንስቶ ተናጋሪ ጉቶ ያደረጋቸው ገዢ መንግስት መሆኑን ረሱት እንዴ? ትንሽ ከረም ስላለ ረስተውት ካልሆነ እሳቸውም ከደቡብ ክልል እንዴት እንደተባረሩ ያውቃሉ እኮ፡፡ አለቆቻቸው አላማቸውን ለማስፈጸም ያዘዙዋቸውን ሰርተው ሲጨርሱ ነው ብቃት ማነስ የሚል ታፔላ የተለጠፈላቸው፡፡ ዛሬ እሳቸውም ወንጅሉ ስለተባሉ ይህን ያህል ማለታቸው ይገርማል፡፡ ምነው ትላንትን ረሱት፡፡ ቤንሻንጉል ጉምዝ ብቻ ነው እንዴ አማራውን ያባረረው? ደቡብ ክልልስ? ወያኔ ታሪካዊ ጠላቴ ባለው አማራ ላይ የሚከሰቱ አዲስ ድርጊቶች አይደሉም እኮ እነዚህ፡፡ ይልቅ ባለስልጣኖቹን ከሚያባርሩና ከሚሳደቡ ወያኔ አማራ ላይ ያለውን ጥላቻ  እንዲፍቁ አለቆቻቸው ቢጠይቁ አይሻልም?

Thursday, April 18, 2013

“ማሪያም ነኝ” ባዩዋ ተፈረደባት

“ማሪያም ነኝ” ባዩዋ ተፈረደባት

በአሸናፊ ደምሴ
የፌዴራሉ አቃቤ ህግ የማይገባትን ጥቅም ለማግኘት
በማሰብ በተለያዩ ጊዜያትና ቦታዎች በመንቀሳቀስ
ሰዎችን በማታለል “እኔ ማርያም ነኝ፤ እንደኢየሱስም
በጅራፍ ተገርፌያለሁ፤ ከሞትም ተነስቻለሁ፤
የወለድኳቸውንም ልጆች ያገኘሁት በመንፈስ ነው”
ስትልና የዓለም ፍፃሜ ደርሷል በሚል የሰዎችን የግል
ሀብት ለራሷ ስታደርግ ደርሼባታለሁ ሲል ክስ
የመሰርተባት የ34 ዓመቷ ትዕግስት ብርሃኑ ወ/
ጊዮርጊስ፤ በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 6ኛ ወንጀል
ችሎት ፊት ቀርባ ጥፋተኛ ሆና በመገኘቷ በ2 ዓመት
ከ4 ወራት ፅኑ እስራትና በአንድ ሺ ብር የገንዘብ
መቀጮ እንድትቀጣ ሲል ባሳለፍነው ሳምንት ወሰነ።


እንደአቃቤ ህግ የክስ ዝርዝር ከሆነ ግለሰቧ በአራት የተለያዩ ክሶች የተወነጀለች ሲሆን፤ የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት
“ለሰው ህይወት ማለፍ ሳቢያ ነች” ሲል አቃቤ ህግ ያቀረበውን ክስ ያልተሟላ ነው ሲል ውድቅ ሲያደርገው በተቀሩት
ሶስት ክሶች ግን ጥፋተኛ ነች ብሎ እንድትከላከል ብይን ሰጥቶ ነበር።
ተከሳሿ ጥፋተኛ የተባለችበት አንደኛ ክስ በየካቲትና በመጋቢት ወራት ውስጥ 1999 ዓ.ም የማይገባትን ጥቅም

ለማግኘት አስባ በጉለሌ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 21 ልዩ ቦታው ኪዳነምህረት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከ300 በላይ
ሰዎችን በመሰብሰብ “እኔ ማርያም ነኝ፤ እንደኢየሱስም በጅራፍ ተገርፌ፤ ከሞትም ተነስቼያለሁ” የሚል የሀሰት ወሬ
በመንዛትና የዓለም ፍፃሜ ደርሷል ንብረት አያስፈልግም በሚል ያላችሁን ንብረት አምጡ ስትል ከተለያዩ የግል
ተበዳዮች ጥሬ ገንዘብና ወርቅ የተቀበለች ሲሆን፤ በአጠቃላይም 40ሺ ብር ለግል ጥቅሟ አውላለች ሲል በክስ መዝገቡ
ያስረዳል።
እንደአቃቤ ህግ ቀጣይ ክስ ደግሞ ተከሳሿ በሰኔ 1 ቀን 1999 ዓ.ም በየካ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 16 ልዩ ቦታው
ላምበረት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ 50 የሚደርሱ ሰዎችን በመያዝ ወደደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን በመጓዝ ወንጭ
ገዳም ተብሎ ወደሚጠራው መንፈሳዊ ቦታ በመውሰድ በፆምና ፀሎት ሰበብ አብረዋት የነበሩት ሰዎች ለአምስት ቀናት
ምግብ እንዳይበሉ በማድረግ እንዲዳከሙና ለከፋ ጉዳት እንዲዳረጉ አድርጋለች ሲል በክሱ ያትታል።
በሌላም በኩል ግለሰቧ በጥር 24 ቀን 2003 ዓ.ም በልደታ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 11 ልዩ ቦታው ተክለሃይማኖት ቤተ-
ክርስቲያን ቅጥር ውስጥ ወደ 20 የሚጠጉ ህፃናት ልጆችና ሴት ተከታዮቿን በመያዝ፣ “እኔ ማርያም ነኝ፤ ልጆቼን
የወለድኳቸውም በመንፈስ ነው እንጂ ከወንድ ጋር ተኝቼ አይደለም” በማለትና ተከታዮቿም እርሷ ማርያም ነች።
ሞታም ተነስታለች እንዲሁም 40 ቀን ያለምግብ ትፆማለች በማለት ሀሰተኛ ወሬዎችን እንዲነዙ በማድረግ
ስታስተምር እንደነበር ከፖሊስ የምርመራ መዝገብ ደርሶኛል ያለው ዐቃቤ ሕግ፤ በዚህም ምክንያት በቤተ-ክርስቲያኗ
ቅጥር ግቢ ውስጥ የነበሩ ሌሎች ምዕመናን “ ሀሰት ነገር አትናገሪ” ሲሉ በመቃወማቸው ወደሁከት ውስጥ እንዲገቡ
ያደረገች በመሆኑ በፈፀመችው የሀሰት ወሬዎችን በማውራትና ህዝብን በማነሳሳት ወንጀል ተከሳለች ይላል።
ጉዳዩን ሲመረምረው የቆየው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 6ኛ ወንጀል ችሎትም የዐቃቤ ሕግን ክስ ተከሳሿ
ማስተባበል ባለመቻሏ ጥፋተኛ ሆና አግኝቻታለሁ ሲል፤ መጋቢት 25 ቀን 2005 ዓ.ም በ2 ዓመት ከ4 ወር ፅኑ
እስራትና በ1000 ብር እንድትቀጣ ሲል ወስኖባታል።¾
ምንጭ፡ ሰንደቅ ጋዜጣ

Monday, April 1, 2013

ሳውዲ አረቢያ በዘመቻው የሚፈናቀሉት ዜጎች አሳሳቢነትና የእኛ ምልጃ.

ይህንን ጽሁፍ የወሰድኩት ነብዩ ሲራክ ከጻፈው የማለዳ ወግ ከሚለው ጽሁፍ ላይ ነው እና አዎ ይህ የሁላችንም ምልጃ ”ልመና ” ነው እባካችሁ ስሙን ለቦንድ እና ለተለያዩ ነገሮች ስትሰበስቡን እንደምንሰማችሁ እናንተም ዛሬ ስሙን በሳኡድ አረቢያ የሚኖሩ ኢትዮጵያኖች ድምጽ…………..
በዘመቻው የሚፈናቀሉት ዜጎች     http://freedom4ethiopian.wordpress.com/2013/04/01/65476/

እኔም እንዳቅሜ ሚጢጢዬ ትዝታ ፑሽኪን ውስጥ አለኝ፡



ወዳጄ አደም ሁሴንን የፑሽኪን ትዝታህ ሳየው ምላሽ ልሰጥ ግድ አለኝ፡፡ እኔም እንዳቅሜ ሚጢጢዬ ትዝታ ፑሽኪን ውስጥ አለኝ፡፡ ጋሽ አያልነህን በብዙ ነገር አድናቂው ብሎም አክባሪው ነኝ፡፡ ብዙ አማተር ገጣሚያን ያጡትን መድረክ አዘጋጅቶ እንኩ ያለ…ለጥበብ ስለጥበብ ብዙ የደከመ ነው፡፡ በተለይ ተተኪ ተዋንያን እና ገጣሚያን የማውጣቱን ነገር የእሱን ያህል የሰራ፣ የደከመ አላየሁም፡፡ ይህንን ስል የጋሽ ተስፋዬ አበበን ውለታ ረስቼ አይደለም፡፡ ጋሽ ተስፋዬ(ፋዘር) ራሱን የቻለ ቦታ ያስፈልገዋል፡፡
   አንቱ የተባሉትም ለወጣቶች እውቀታቸውን እንዲያካፍሉ እና እነሱም እንዲከበሩ ለማድረግ ወርሃዊ የግጥም ምሽት  ማዘጋጀቱ በልቤ ውስጥ ቦታ እንድሰጠው ያደረገኝ ነገር ነው፡፡ ስንቶችንስ ለቁም ነገር አድርሷል? ስንቶች ከትላልቆች ትምህርት እንዲቀበሉ አድርጓል? እናንተው መልሱት፡፡ እኔ ጽሁፌን ሳሳየው አንተ ጸሀፊ የመሆን ተስፋ የለህም ያለኝ ታዋቂ ደራሲን ሳስታውሰው ያናድደኛል፡፡ እሱን ለማግኘት የደከምኩበትን ጊዜም ሳስብ ያበሳጨኛል፡፡ በእርግጥ እሱ በሰጠኝ አስተያየት ተስፋ አልቆረጥኩም፡፡ ይባስ ጠነከርኩኝ፣ እልህ ተጋባሁኝ፡፡ እነዚህ አይነት አማተርን የሚያጫጩ ባሉበት ቦታ ጋሽ አያልነህን ማየት ምንኛ መታደል ነው፡፡
አደም ሁሴን ‹‹..አርቲስት ጥላሁን ገሰሰም አንድ የጋሽ አያልነህን ቲያትር ይሰራል እየተባለ በምን ምክንያት እንደቀረ አላውቅም ወይም ስራ እንዴ…? …… ብቻ ግን ያስቆጫል አንድ ቲያትር ተውኖ ቢሆን ኖሮ እንዴት ደስ ይል ነበር…….!›› ብለህ ነበር በዝክረ-ጽሁፍህ አዎ! ተብሎ ነበር፡፡ ግን አልሰራም፡፡
አንደኛ ጋሽ አያልነህ ካለበት ተደራራቢ ስራ አንጻር በወቅቱ ቶሎ ጽፎ መስራት አልቻለም፡፡ ሁለተኛ ጥላሁንም በተለያየ ወቅት ለስራ፣ ለህክምናም በተደጋጋሚ ወደ ውጭ ይወጣ ነበር፡፡ በኋላም እግሩ ላይ ችግር ከመድረሱ ጋር ተከትሎ ነገሮች አልተገናኝቶም እንደሚሉት ሆኑ፡፡ ‹‹..ግን ያስቆጫል አንድ ቴያትር ተውኖ ቢሆን እንዴት ደስ ይል ነበር..››ላልከው ሁለት ቴያትሮች ሰርቷል፡፡
በ1946 እና በ1947 ሀገር ማህበር በነበረበት ጊዜ ‹‹መንገደ ሰማይ›› እና የሁለተኛውን ርዕስ በደንብ ባላስታውሰውም ‹‹የተኮነነች ነፍስ›› ይመስለኛል፡፡ ሁለቱም ላይ በብቃት የተውኖ እንደነበር የሞያ ጓደኞቹ 60ኛ አመቱን በሀገር ፍቅር ባከበረበት ወቅት ገልጸዋል፡፡         

Friday, March 8, 2013

የሞት ጉዞ
 ልጠይቅህ ለማይረባ ስደትህ መሞት ለምን አስፈለገህ?
በነዛር ዳግ ተጻፈ…
ይህንን ጥያቄ የምጠይቅ ወንድሜ ከልብ ሆነ እንድትሰማኝ እፈልጋለ፡፡ ያለኸው የትም ይሁን የት ቢያንስ ትንሽ ጥያቄ እና መልዕክት አዘጋጅቼ ካለሁበት ቦታ ላይ እኔው ስደተኛ ወንድምህ እንዲህ እልሃለ ፡፡ በደንብ ስማኝ ወንድሜ በየትኛውም የስደት ስሜት ላይ ሁን ችግር ላይ ጥያቄዬን እንድትመልሰ እለምንሃለ፡፡

        አሁን ያለኸው ምኑንም በማታውቀው ሰሜት ውስጥ ሆነ ሰደት..ሰደት የሚለውን የልብህን ትርታ እያዳመጥክ ይሆናል፡፡ ወይም ደግሞ ከገባህበት የኑሮ አዘቅት ውስጥ ለመውጣት በምን በኩል አድርገህ አገሩ ጥለህ እንደምትወጣ  እያሰብክ ነው፡ በጎንደር ሱዳንን አለያም ቀይ ባህርን እንደምትሻገር፣ ሶማሊያን እንደምታልፍ እና የተሰፋው ምድር አረብ አገር እንደምትገባ ልብህ ሻቅሏል፡፡ እዛም ለመግባት ልብ እንዲጀግን፣ ወንድነት ዘራፍ እንዲል ከዘመድ፣ ከጎረቤት ከአካባቢ ከምታውቃቸው ሰዎች ውስጥ ያሳለፉትን የባህር ጉዞ ገድል ደጋግመህ አሰበሀል፣ ሰምተሃል፡፡ እነሱም የነገሩ ጥሩ እንጂ ችግሩን ስላልነገሩህ አንተም ከማን አንሳለ ብለህ መንገድ ለመጀመር አኮበኮብክ፡፡
 
        ከዛ በፊት ግን እነሱ ያልነገሩህን እውነታ፣ የሸሸጉትን ጉድፍ ላውጋህ..ምስጢር ያደረጉትን ታሪክ ላንቆርቁርልህ፡፡  የደረሱበትን ሰቃይ ያሉበትን ችግር እኔም ካለሁበት ቦታ ሁኜ ያየሁትን እርግጠኛ ሆኜ የሰማሁትን ደሞ መረጃ ፈልጌ እነግርሀለ፡፡ ታዲያ ስታነብ ነገሩ ፍየል ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ ቢሆንብህ አይገርመኝም፡፡ ሙት ነው የምልህ አንተ የሰማው ነገር ሌላ ተኩሎ ተሽሞንሙኖ..አምሮ ነው፡፡ ያለው ሀቅ ደግሞ ተገልብጦ እንደሻማ በርተህ እንደቆሻሻ ተገፍተህ ነው፡፡
     አንተ ለመሰደድ አስበህ ተዘጋጅተህ ያለኸው እንዴት እንደምትሰደድ እንጂ ሰለምትከፍለው ሞት አይደልም ፡፡ ሞት እንዳለ ሰምተ ቢሆን እንኳን ቀኔ ከደረሰ ልሙት የሚለውን ደካማ አባባል ታጉተመትማለህ፡፡ እግዚአብሄር ያውቃል ብለህ እሳት ውስጥም ትገባ ይናሆል፡፡ እግዚአብሄር ግን እርዱኝ እረዳችኋለሁ አለ እንጂ ገደል ግቡ እኔ አወጣችኋል አላለም፡፡ ካለበለዛ ግን ልብ በል ተረት ይዘህ ተረት ሆነህ ነው የምትጓዘው፡፡ እሱም ይሁን ግድ የለም:: ዋናው የሰቆቃ ቦታ ስትገባ ሞት አሰር አጅ ጣዕም እንዳለው የምትረዳው ብዙም ሳትቆይ ጀልባ ላይ የሚያሳፍሩ በመኪና አፍነው የሚጭኑህ…በረሀውን ስምንትነሰ ዘጠኝ ቀን በእግር የሚነዱህ አረመኔ ደላሎች እጅ ስትገባ ነው ሞትን የምትመርጠው፡፡

     እመነኝ እየነገርኩ ያለሁት ገና አገርህን ብሎም አህጉርህን ጥለህ ሳትወጣ ሰላለው ሀቅ ነው፡፡ መቼም ለመሰድድ የተነሳ ልብ በአገሩ ወርቅ ሲዘንብ ቢያይ እንኳን ሊሰደድበት ያሰበው አገር ገብቶ የበለጠ እንቁ ይዞ መመጣት እንጂ አገሩ ላይ የሚዘንበው ወርቅ ለሱ መዳብ ነው፡፡ አንተም ምንም ቢኖርህም ያለህን ሸጠህ ተበድረህ ወደጉዞ ወደ ህልም አለም ታደርጋለህ፡፡ ሙት ህልም ነው፡፡ ገነት አድርገህ የሳልካት ሲኦል ሆና ትጠብቅሀለች፡፡ በውሸት ዝና ሰምተህ የተስፋ ምድር ወዳደረካት ሀገር ለመግባት ስትሰናዳ የሚያገኙህ ደላሎች አንተን በእጃቸው እስኪያሰገቡ አፈ ቅቤ ናቸው፡ የተሸከምከውን ገንዘብ እስኪረከቡ ድረስ ወዳጅነታቸው ልዩ አሳቢነታቸው ከእናት ልጅም በላይ ሆኖ እምነት ለእነሱ ልዩ ይሆናል፡፡ እነሱን ከሁሉም አሰበልጠ ልትመለከታቸው የምትሄድበትን ባህር የሚከፍሉ አድርገህ ልክ እንደ ሙሴ ልታያቸው ትችላለህ፡፡ ሙሴ የሰራውን ታላቅ ታምር ሰለምታውቅ፡፡

     ቤተሰብህን ተሰናበተ ከእናትና አባትህ ምርቃት ተቀብለህ ጉዞውን በመረጥከው መንገድ አድርገህ ወደ ስደት ሰትወጣ የሚታይ ሁሉ ሌላ ው፡፡ ገንዘብ፣ ወርቅ፣ ገና መድረሻህን ሳታውቅ ምን መሰራት እንዳለብ ታስባለሁ፡፡ ይሄ የሆነው ደግሞ ባህር አሻጋሪ ደላሎች የነገሩህን ነገር፣ የሰጡህን የተሰፋ ክምር ሰለምታስብ ነው፡፡ እነሱ ስራቸው አንተን ከተሳካላቸው አሻግረውህ በመሸጥ ካልሆነም ካንተ በድለላ ሰለሚያገኙት ገንዘብ እንጂ ያንተ ሞት ለነሱ ምናቸው ነው? ምናቸውም አይደለም፡፡ አንተ ብትሞት ካንተ ያልተማረ እውነቱ ያልተዋጠለትን ደግሞ ይወስዳሉ፤ ይሸጣሉ፡፡ ለዚህም ሲሉ እውነቱን የሚነግሩህ እንዳይመስልህ፡፡ አረብ ሀገር ገብተህ ሰለምታገኘ ገንዘብ፣ ሰለምትዝቀው ወርቅ እንጂ ሰለሚደርስህብ ሰቃይ ባህር ላይ ከነህይወት ሰለመጣል፣ በበረሃ ሰለመንከራተት እንዲሁም ሰለሞት አያወሩህም፡፡ ይህን ለምን አልነገሩኝም ካልክ ግን እውነትም ሞኝ ያውም በህይወቱ ቅልልቦሽ የሚጫወት ሞኝ ነህ፡፡ የተገለበጠ የነገር ታሪክ ውስጥ ራስህን የምታገኝው ጀልባዋ አንድ  ኪሎ ሜትር ሳትሄድ ነው፡፡ ወይም የተሳፈርክበት መኪና ከተማ ጥሎ እስኪወጣ ነው ያለው እውነታ ይህ ነው፡፡ አንተ ደግሞ የሰማህው ይህ አይደለም ፡፡ አይንእያየ ትደበደባለህ፣ ስደት ሴት ያደርግል፡፡ ትራባለህ፣ ትደፈራለህ፣ ብልት ይቆረጣል፣ ከባሰም ከነነፍስ ወደ ባህር ትወረወራለህ ወይም ትሰቀላለህ፡፡ ለዚህም  ምስክር የሚሆን ሰው ብታገኝ አታምንም፡፡ ራሱ የምትወረወርበት ባህር አፍ አውጥቶ ካልተናገረ…አረ ቢናገርም አታምነውም፡፡

    እየደረሰ ያለውን በደል እና ሰቃይ ችለህ ወደምትሻገርበት አገር ለመግባት ትጓዛለህ፡፡ ሶማሌ አልያም የመን ልትገኝ ትችላለ፡፡ የባሰ ደግሞ ጅቡቲ ከጣህ..፡፡ በቃ! እዚህ አካባቢ ያለው ሁሉ ጨለማ ነው፡፡  ብትጮህ የሚሰማ የለም፡፡ የሚደርስ የለም፡፡ ሁን ያሉህን ትሆናለ አድርግ ያሉሁን ልታደርግ ትችላለ፡፡ አሁንም ለእዚህ ማሰረጃ የምነግር የሩቅ ጊዜ ተሞክሮ ሳይሆን በቅርቡ አሁን በቅርቡ የመን ላይ እየሆነ ያለው ነገር በቂ ነው፡፡
     ምን ያህል ዜጋ የመን ላይ ያልተገደበ ስቃይ፣ በደል፣ ግፍ፣ እየደረሰባቸው እንደሆነ በእዚህ ክፍለ ዘመን ሊደረግ ቀርቶ ሊታሰብ የማይችል አሰቃቂ ነገር በወንድም በእህቶቻችን ላይ እየደረሰ ነው፡፡ በጥቂት ኢትዮጵያዊያን እና የአረብ ዜጎች ገንዘብ አምጡ ተበለው ታፍነው በበረሃ አየሞቱ የወሲብ ሱስ ባናወዛቸው ሰዎች የሚደፈሩ ሞልተዋል፡፡ በቁማቸው በእሳት የሚቃጠሉት የማንም ዜጎች ሳይሆኑ የአንተው ሀገር ልጆች ናቸው፡፡ እነሱም ከሀገራቸው ሲወጡ እንዳንተው ብዙ ህልም ይዘው ነው፡፡ የተገኙት ግን በመቃብር አፋፍ ላይ ነው፡፡ ታዲያ ከዚህ በላይ ሞት ምንድነው? ይሄ ሞትስ ለማን ነው? አንተንም የምጠይቀው ይህንን ነው፡፡

   እድለኛ ሆኖ ዕድል ቀንታው ሳውዲ አረቢያ፣ ዱባይ ኩዌት ብቻ አንዱ የነፍስህ መሻት የወደደው አገር ላይ ገበተሀል መቼም ከተራራ በላይ የሆነ መከራ፣ ሰቃይ አልፈህ ሰለመጣ ባለመሞት አምላክን አመስግነህ ሊሆን ይችላል፡፡ ያለፍከው ግን ሂደት እንጂ ውጤት አልነበረም፡፡ እንኳን በህገ-ወጥ መንገድ ሀገራቸው ገበተህ፡፡ በህጋዊ መንገድ ለገባው ስደተኛም የማይመቸው የአረብ ምድር የተደላደለ ኑሮ ህይወት ይሰጥሃል ልል አልችልም፡፡ የሰማህው ነገር ሁሉ ከንቱ የሚሆንብህ ሀገር ያለህን የሰውነት ሰሜት ሰታጣ በምድረ በዳ የሳልከው ስዕል ስታሰበው እውነትም ያኔ ስንት ሞት እንደሞትክ ይገባሃል ፡፡

   መኖሪያ ፈቃድ የለ፡፡ ገንዘብ የለ፡፡ ቤት የለ ምንም ሁን ብቻ ሰትገኝ ምን ስህተት እንደሰራህ ይገባሀል፡፡ ከፖሊሰ ጋር አይጥ እና ድመት ስትጫወት በራብ ስትቆላ በውሃ ጥም ስትቃጠል ምሬቱ ያኔ ይገባሀል፡ እንዲሁም እርግጠኛ ሁነህ ሰራ ብታገኝ እንኳን ሰለማይከፈልህ ደሞዝ ስታሰብ ማበድ ትጀምራለ፡፡ ብሶትህን ለሰው አታወራ አጠገብ ሊኖር የሚችለው የምትጠብቅ ግመል ወይም የምታጥበው መኪና ብቻ ነው፡፡ አሁን አንድ ነገር ይገለጽልሃል፡፡ ያለህበት ምድር ዝናብ የሌለው ደመና እንደሆነ ሁሉ የአንተ የስቃይ እና የብሶት ጩኸት ለአረቦች ምንም እንዳልሆነ አስብ፡፡

    ቀጥለህም ህልምህን ታሰባለህ፡፡ ለቤተሰብ የገባሀው ቃል፣ ልትገዛ የወጠንከው መኪና፣ ልትሰራ ያሰብከው ቤት፣ እነዚህ ሁሉ በአይነ ህሊና ይመላለሳሉ፡፡ ትንሽ ካሰብክ የሰማኸው ታሪክ የዘመድ፣ የጎረቤት፣ የአብሮ አደግህ ሁሉ ትዝ ይልሃል፡፡ እሱ ትዝ ሲልህ ከራስ ጋር እልም ያለ ፀብ ውስጥ ትገባለ፡፡ የሰማኸው ይህ ሰላልሆነ ግር ማለትብቻ ሳይሆን ታበረዳለህ፡፡ አብሮ አደግህ ደብዳቤ ጽፎ ዘመድህ ስልክ ደውሎ የነገሩ ሁሉ ግራ ይገባሃል፡፡ ተበድረህም ተለቀትህም ተሰደድ፡፡ ሳውዲ ዱባይ ግባ፡፡ ሰራ በሽ በሸ ነው ገንዘቡ ተቆጥሮ አያልቅም ያሉህ ይህን ስላልሆነ ታስባለህ፡፡ የገዙትን ቤት እና መኪና ወይም አንዱ ህንጻ ስር ተነሰተው የላኩትን ፎቶ ታስታውሳለ፡፡ በዚህ ነው ከራሰ ጋር ብጥ ብጥ ውሰጥ የምትገባው፡፡
ሁሉም መራራ የሚሆንብህ ደግሞ ስንት ጊዜ ከሞት ጋር እንደተፋጠጥክ ስታሰበው ነው፡፡ ምን አልባት ክው ብለህ ልትቀር ሁሉ  ትችላለህ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ሞትን በአይን አይተኸዋል፡፡ ከዚህ ሁሉ ታሪክ ወጥተህ ራስህን የምታገኘው ህልም የማይፈታበት ምድረ በዳ ላይ ነው፡፡ ወይ አትወጣ ወይ አትገባ፡፡

  እዚህ ጋር ሳልነግር የማላልፈው ሃቅ ሀገር ሁነህ የሰማሀው እውነታ እና ወዳጆችህ ያሉት የሰማይ እና የምደር ያህል የተራራቀ የሆነው በምን መሰለ፡፡ ምን አልባት እነሱ እድለኛ ሆነው ወይም በሌላ መንገድ ሂደው ካልሆነ በሰተቀር ሀገር ገዝተው ያየኸው ነገር ሁሉ ሰርተው እንዳላመጡት እኔም ምስክር እሆናለሁ፡፡ አንተም ጨክነህ በራስህ ፈርደህ ከመጣህ እውነታውን ትረዳለ፡፡
 
     እውነቴን ነው ያልኩህ አንተ ግን ይሄኔ ራሱ እዛ ተቀምጦ እኔን አትምጣ ይላል ብለህ ብታሰብ መብትህ ነው፡፡ እኔ እያልኩ ያለሁት ቢያንስ በሞት መንገድ አትጓዝ፡፡ የምትከፍለው ዋጋ እና ሞት ለማን እንደሆነ ደጋግመህ አሰብበት፡፡ ከዛም ሰትሰደድ ቢያን በእውነተኛው መንገድ ውጣ ነው የምል፡፡ ቢሆንም ባይሆንም ሁሉም  ነገር ዘግይቶ ይገባሃል፡፡ ያኔ በጸጸት እሾህ ትጠቀጠቃለህ፡፡
 
     እይ ወንድሜ የምነግር ነገር አንድም ሀሰት የሌለው እውነታ ነው፡፡ የነገርኩ ግን ሁሉንም አይደለም፡፡ ሁሉም እውነታ እንደምትጓዝበት ባህር የሰፋ ስለሆነ ነግሬህም አውርቼም አልጨርስም፡፡ እያልኩ ያለሁት ቆም ብለህ ደግመህ ደጋግመህ አሰብ ከዛ የሆነውን ተቀበል፡፡ መንገዱ አድካሚ ቢሆን አንኳን ባትጠቀምም ትደርሳለህ፡፡ ከዛ ትክክለኛው ቦታ ስትገኝ አንተም ታሪክህን ትተርካለህ፡፡ የባህር ስቃይህን የበረሀ ውሃ ጥምህን ትናዘዛለህ፡፡ ከዛ በኋላ ሞትህን ስታሰበው መንገድ ላይ ሞተው ቀብራሃቸው ሰለመጣኸው እንዳንተው ስደተኞች አሰብ፡፡ መንታ መንታ እንባ ታለቅሳለህ፡፡ በማልቀስ ዝም አትልም ይህን ሁሉ ዋጋ የተከፈለው ለማን እንደሆነ ይሄ ሞትሰ ለምን / ለማን እንደመጣ ቢደላህም ባይደላህም ስታሰበው ትኖራለህ፡፡
  
    እኔም ይሄንን ሞት የከፈልከው ለማን እንደሆነ አጠይቅሃለ? ማብቂያውስ ምንድነው? አሁን ለጊዜው ለአንተ የምለው ይህን ይመሰላል ፡፡ ከውቂያኖሱ ጨልፌ የነገርኩህ ፡፡
   ቀጣይዋ ያንተው እህት (እህቴ) ናት ፡፡ እሷንም ይሄ ሞት ለማን እላታለሁ፡፡
ይቀጥላል ፡፡