Wednesday, October 10, 2012

« ሐዋሊን ፡ ሳስበው ፡ ሳስበው » ሁለት ፡፡

by Nezar Dage on Sunday, June 3, 2012 at 5:20am ·
                                   ሐዋሊን ሳስበው ፡ ሳስበው ፡፡

                                     ሁለት ፡፡
   ባለፈው የቆመንነው ወደ ሐዋሊ ለመግባት እየተንደረደርን ፡ በተለያዩ ታክሲ እና መንገዶች ሰለሚገጥማችው ገጠመኞች አውግተን ነው ፡፡  ያለነው አውን ገና ከ ሐዋሊ ደጃፍ ነን ፡፡ ዛሬ ዘው ብለን ወደ ሐዋሊ ከመግባታችን በፊት አንድ የምናየው ቦታ አለ ፡፡ አናንተ ባላችውበት ሆናችው እንድትከተሉኝ ለጊዜው አካላችውን ከተመቻችው ቦታ አንዱ ጋር አሳርፉት አና በህሊናችው ግን እኔን ተከተሉኝ ፡፡
    መንገዱን ጀምረናል ፡፡ የምንሄደው ወደማናውቀው ቦታ ወይም ዐገር አይደለም ፡፡ ተወልደን ወዳደግንበት ፣ ከፉ ደግ ወዳየንበት ፣ በጣም ወደምንወዳት ዐጋረችን ነው ፡፡ እዛ የተወሰነ ቆይታ አድርገን እንመለሳለን ፡፡ መቼም ሰለ ሐዋሊ አያወራን ወደ ኢትዮጰያ መሄዳችን ያሰገርማችው ይሆናል ፡፡ የምናየውን እና የምንታዘበውን ነገር አይተን ስንጨርስ ወደ ኢትዮጵያ የመሄዳችን ሚስጥር ይገባችዋል ፡፡

    እይታችንን እንጀምራለን ፡፡ አዎ ብዙዎች ትላንትም ሆነ ዛሬ ያለባቸውን ችግር ሊፈቱ ፣ ሰርተው ሊለወጡ አስበው ፡ ሰደትን መፍቴ አድርገው እራሳቸውን ለሰደት ያዘጛጁ ወጣቶችን ፡ በተለይም ሴት እህቶቻችን ዋናውን ቦታ ይይዛሉ ፡፡   ሁሌም በሚኖሩበት ነገር ያለው ሀቅ ቢከብዳቸው ፣ በአቅማቸው ሊጋፈጡት የሚችሉት ነገር  ሰደት ነው አና. እራሳቸውን በሰደት መንገድ ላይ ሲያቀርቡ ያለምንም ማመንታት ነው ፡፡
  በፍቅር የኖሩበት የቤተሰባቸው ህይወት ፈርሶ ፣ ብዙ ያሰለመዳቸው የአባታቸው እጅ ታጥፎ ፣ ወደር የሌለው የእናታቸው ደግነት በችግር ተሸንፎ ማየት የሚከብዳቸው ፡ ወንድሞቻቸው ፣ እሆቻቸው ፣ ሲልም ፍቅረኞቻቸው እና የትዳር አጋራቸውን የጎበጠ ኑሮ ለመለወጥ ፡ ከማንም በፊት የሰደትን መንገድ ጀማሪዎች
የዛሬ የሐዋሊ እውነታወች ናቸው ፡፡

    በአገራቸው ቆመው ያሰቡትን ለማሳካት ፡ ሰርተው ጥረው ቤተሰብን ለመቀየር ካላቸው ፍላጎት አንጻር ፡ ምንም ባህላቸው ከባህላቸው ከማይዛመድ ህዝቦች ጋር
ቋንቋቸው ፡ ምንም ከማያውቁት ቋንቋ ተናጋሪዎች ጋር ለመኖር ወስነው በአይናቸው እንባ እያነቡ ሲወጡ ያኔ የድህነት መጥፎ ጎኑ ቁልጭ ብሎ ይታያል ፡፡  እያየን ያለነው ከመነሻው እዛው አገራችን ያለወን የዜጎቻችን የኑሮ ነጸብራቅ ነው ፡፡ በዚ አድካሚ የህይወት ጉዞ ፡ መድረሻቸውን ሳያውቁት ፡ ሻንጣቸውን አንጠልጥለው ፡ ከፈጣሪ ጋር ወደማያውቁት አለም ፡ አረብ ፡ አገር የሚጓዙትን   ህልመኞች እናስባቸው ፡፡
      ከአገራቸው ሁሉም ሰደተኞች ሲወጡ ይዘው የሚወጡት ተሰፋ ነው ፡፡ የነገ ትልቅ ህልም ፡፡ ይህንን ህልም ለማሳካት መውተርተር ፣ መባዘን ፡፡ ከምንም በላይ የሚያማቸው ቃል አለ ፡፡ በነሱ አንደሻማ መቅለጥ ፡ ብርሃን ሊሆኑት ያዘጋጁት ቤተሰበብ ፣ አደራ ፣ ፍቅር ፡፡  የእውነታው ግብ ግብም እዚ ይጀምራል ፡፡
    አውን ያለነው አንድ በችግር የተጎሳቆለ ቤተሰብ መሀል ፣ ድህነተ/ የበዛበት ሰፈር ውስጥ ነን ፡፡ እናንተ ህሊናችው የፈቀደውን ቦታ እዩ ፡፡ በዚ በችግር በተጎሳቆለ ቤተሰብ ማህል ፣ ችግር የውቂያኖስ ያህል የሰፋበት ማህበረሰብ ፡፡   ከዚ ማህበረሰብ ውስጥ   በአረብ ፡ አገር ሰደት ፡ ለመለወጥ ያኮበኮበች የትንሽ ልጅ ልብ ፡፡

     በማታውቀው አገር ልትኖር የገዛ ዐገፘ እንጀራ እናት ሰትሆንባት ፡ የማታውቀውን ያን ማዶ አዚ ሁና ዘውትር በሀሳብ አየቃኝችው ፡ መሽቶ በነጋ ቁጥር በሰደት ሃሳብ ኖራ በሰደት ታደራለች ፡፡ የዛች እጻን የልብ ትርታ ሚስጥሩን የሚያውቀው የቅርቧነው ፡፡ እሷ ግን በዚ ሁኔታ ማለፍ አትፈልግም ፡፡ እንደ ጉም ለተነነው ለቤተሰቦቿ ማንነት ሰትል በማታውቀው አገር ጅብ ቢበላትም ትመርጣለች ፡፡ ከፊትም ከዋላም ያለው ነገር ሁሉ አሰፈሪ ነው ፡፡
    ዐገሯን ማሰብ አትሻም ፡፡ በአገሯ የመኖር ህልመም የላትም ፡፡ አሁን አሁን የእሷ አ.ኩያዎች ኢትዮጵያ የነሱ አትመስላቸውም ፡፡ በአንድ አገር ውስጥ ሁለት አገር ፡፡ በታላቅ ህዝብ መሀል ታናናሽ ህዝቦች የሚኖሩባት አሰከፊ ኢትዮጵያ ፡፡   እዚ ጋር ቆም ብለን ፡ ለደቂቃ የሐዋሊ ወጣት ሴቶችን እናስብ ፡ ከነሱ ውስጥ ደግሞ ትናንሽ ህጻናት ፡፡ 

        እቺን መሰል የአገራችን የዘመን ውጤቶች ፡ ቦሌ ኤርፖርት ሲገቡ የሚያነቡት በቃ ተለያየን እንባም ፡ ሳይፈልጉ መለየትን ፣ የወዶ ማጣትን ህመም እያሳየን ፡ አላማ ነው እና አገራቸውን እንደዘበት ጥለው ይወጣሉ ፡፡ አገራቸውን ጥለው በሚወጡ ዜጎች ልክ ፡ ብዙ ችግር ፣ ብዙ ስቃይ አለ ፡፡  በየቤቱ በየጓዳው እውነት የማይመሰል ፡ አሰከፊ ድህነት አለ ፡፡  የዚ ድህነት ቀንበር ተሸካሚዎች ደግሞ እነዚው እንቦቅቅላ ህጻናት እና ወጣት ሴቶች ናቸው ፡፡
      ሰለምታውቁት ኑሮ ብዙ አልልም ፡፡ ሁላችንም በየቤታችን ያለውን ድህነት እናውቀዋለን ፡፡ የዚ ድህነት ዋጋ ከፋይ ማን እንደሆነም እንረዳለን ፡፡ የማንረዳው ነገር ቢኖር ዋጋ የሚከፈልበት ገንዘብ አንዴት እንደሚመጣ አለማወቃችን ነው ፡፡
     አውን ወደዋናው ሀሳባችን ልንመጣ ነው ፡፡ የቤተሰብን ኑሮ ለመቀየር በየአረብ አገሩ የሚኖሩ ዜጎቻችን ፡ አንደምን እየኖሩ እንደሆነ ገንዘቡንስ እንዴት እያመጡ እንደሆነ ምን ያህሉ ቤተሰብ ያውቃል ፡፡ የዛን ማዶ እውነታ ሳያውቅ ፡ እህቴ በደወለች ፣ ፍቅረኛዬ በላከች እያለ ምንዱባን እየጠበቀ የሚኖረው ወጣትስ ፡ እውን ገንዘቡ እንዴት እንደሚመጣ ያስበዋል ?
  ልጄ በአመቷ አረብ ፡ አገር ሂዳ ታከሲ ገዛች ፣ ቤት ሰራች ፣ ወርቅ በወርቅ ፣ ገንዘብ በገንዘብ አንበሻበሸችኝ ብሎ የሚኖረው ቤተሰብስ ፡ የአረቦች ምድር ብር የሚፈልቅበት አገር አድርጎ ነው የሚያየው ወይስ እውነታውን እያወቀ ፡ «  የትም ፍጪው ዱቄቱን አምጪው »  በሚል ተረት የልጆቹን የደም ደሞዝ እየበላ ነው ? የተቀመጠው ፡፡ በርግጥ በልጆቹ ብዙ ቤተሰብ አልፎለታል ፡፡ ከትላንት ጨለማ ወጥቶ ብርሃን አዮቶ ይሆናል ፡፡ ልጆቹ የሚኖሩበትን ህይወት ባያይም ፡ ባይሰማም ፡፡
   የዛሬ የኢትዮጵያ ቆይታችን በተከታታይ ለምናየው ሐዋሊ መሰረት ይሆን ዘንድ ነው ፡፡ በርግጥ የቆይታችን ሚስጥር ከገባችው ፣ አሁን ከሀሳባችው ነቅታችው ፡ ሐዋሊን ማየት አንጀምራለን ፡፡ አደራ የምላችው ግን እስከመጨረሻው የዛሬ ቆይታችንን እንዳትረሱት ነው ፡፡ ሐዋሊ ላይ በቆየን ቁጥር ከፊት እና ከዋላችን የምናያቸው ነገሮች በጠቅላላ መሰረቱ የት እንደሆነ ይገባችዋል ፡፡ 
    በአንዱ ሺሻ ቤት ቁጭ ብላ በሀሳብ የምትናውዝ ፣ በተሰፋ መቁረጥ ማንነት ውስጥ ያለችን አንድ ምስኪን ስታዩ በኢትዮጵያ ካየናቸው አንድ ደሀ ሰፈር ውስጥ ፡ ወደ አረብ ፡ አገር ልትሰደድ ያለችን  ህጻን አስታውሱ ፡፡  ከዛም እሰከመጨረሻው አብረን ከቆየን ፡ ሁሉንም እናያለን ፡፡ ከዛ በፊት ግን አንደዛሬው ድንገት ወደ ኢትዮጵያ አንሄድም ፡፡ ጽሁፉን ከማብቃታችን በፊት ፡ ኢትዮጵያ እንቆያለን ፡፡  እሰከዛው ግን ከዛሬ መልስ ጀምረን ሐዋሊን እናያለን ፡፡  የሐዋሊ ኮከቦች የተባሉትንም ፡ የአገራችንን ልጆች አፍ ለአፍ ገጥመን ሁሉንም ከነሱ እንሰማለን ፡፡  ለአሁን ባለንበት ቦታ ሁነን ቢበቃን እና ሳምንት ብንመለስስ ?
                      መልካም ፡ ሳምንት ፡፡

No comments:

Post a Comment